1. ይዘት
  2. ቀዘፋ
  3. ተጨማሪ ይዘቶች
  4. አብሮ መቅዘፍ
  5. ፍለጋ
  6. ከ 30 ቋንቋዎች ይምረጡ።

 
 
 

 

ዜናዎች | 09.01.2009 | 14:00 UTC

ናይሮቢ-የሳዑዲ አረቢያዋ መርከብ ተለቀቀች

የሶማሊያ የባሕር ላይ ወንበዴዎች ባለፈዉ ሕዳር አግተዋት የነበረችዉን የሳዑዲ አረቢያ ግዝፍ ነዳጅ ጫኝ መርከብ ዛሬ መልቀቃቸዉን አስታወቁ።አግድም ሰወስት መቶ ሰላሳ-ሜትር የምትረዝመዉ ወይም ሰወስት የእግር ኳስ ሜዳ የምታክለዉ መርከብ ሥትታገት መቶ ሚሊዮን ዶላር የሚያወጣ ነዳጅ ዘይት እንደጫነች ነዉ።ከአጋቾቹ አለቆች አንዱ መሐመድ ሰኢድ ዛሬ ለአዣንስ ፍራንስ ፕረስ እንደነገረዉ መርከቢቱ ከነ-ሰራተኞችዋ ቆማበት ከነበረዉ ሥፍራ ተንቀሳቅሳለች።መርከቢቱ ያሳፈረቻቸዉ ሃያ-አምስት ሠራተኞችዋም በጥሩ ሁኔታ እንደሚገኙ የአጋቾቹ አለቃ ተናግሯል።አጋቾቹ መርከቢቱን የለቀቁት ገንዘብ ተከፍሏቸዉ እንደሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ መናገራቸዉ አልቀረም። የተከፈላቸዉን ገንዘብ መጠን ግን አላስታወቁም።አንዳድ የዜና ምንጮች ለአጋቾቹ 3 ሚሊዮን ዶላር ቤዛ እንደተከፈላቸዉ ዘግበዋል።

ተጨማሪ መረጃዎች | 09.01.2009 | 14:00 UTC

የዜና አጠቃላይ እይታዜናዎችን በመላ ማተምያትሙ



 

DW-TV EUROPE live

popXport - Das Deutsche Musikmagazin